FREEDOM 4 ALL ETHIOPIANS

FREEDOM,DEMOCRACY.JUSTICE.AND UNITY FOR ALL ETHIOPIANS …by DANIEL TESFAYE

የወያኔ ግፍ ለከቱን አልፏል!

26351fb59e29fb0a1375427042June 12, 2014
የወያኔ ጉጅሌ ራሱ ከሳሽ፣ ፖሊስና ዳኛ ሆኖ በሚገዛት ሀገራችን ውስጥ የሚያካሂደው ግፍ አንድ ህዝብ ሊሸከመው ለሚችለው በላይ ሆኗል።

የወያኔ ሹማምንትና በዘር ለዝርፊያ የተሰማራው ድርጅታቸው በቅርቡ ደግሞ ስዘርፍ አያችሁኝ በሚል ቁጣ ከአንደበታቸው በላይ ምንም ባልታጠቁ የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ከአካሄደው ጅምላ ጭፍጨፋ አልፎ ግለሰብ ተማሪዎችን በማሳደድ ሰቆቃ መፈጸሙን ቀጥሎበታል። በዚህ ሰአት በርካታ ተማሪዎች በታወቁና ባልታወቁ እስር ቤቶች ታጉረዋል። ብዙዎቹ ከትምህርት ገበታ ካላንዳች ጥያቄ ተባረዋል እየተባረሩም ይገኛሉ።

ከወያኔ ግፎች ሁሉ በእጅጉ የሚዘገንነው ሌሎችን በመወንጀል ማሰቃየትና መግደል በፈለገ ቁጥር ራሱ ወንጀል ከፈጸመ በኋላ ወንጀሉን በሌሎች ላይ ለማመኻኘትና ለመቅጣት የሚጠቀሙበት የሃሳብ ዘዴ ነው።

በአለምያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በተሰበሰቡበት አዳራሽ ውስጥ የደህንነት አባሎች ቦንብ አፈንድተው ጉዳት ካደረሱ በኋላ የሚፈልጓቸውን ወጣቶች ቦንብ ሲያፈነዱና ሲጠምዱ ያዝናቸው በማለት ከዚህ በፊት በዊክሊክ መረጃ እንደተለቀቀው የተለመደ በሰው ልጆች ላይ ሰቆቃ ይፈጽማሉ። ሌላው ቀርቶ ቦምብ አፈነዱ ተብለው የተከሰሱት ተማሪዎች በገዛ ጓደኞቻቸው ላይ ቦምብን የሚወረውሩበት ምክንያት የላቸውም።

ወያኔ ተማሪዎቹን አረመኔና እብድ ለማስመሰል የሰራው የራሱ ትንሽዪ ድራማ ወይም ሌላኛው አኬልዳማ መሆኑ ግልጽ ነው።

ወያኔ ደግሞ እንዲህ አይነት የወሮበላ ስራ እንደሚሰራ እንዳላዪ የሚያዩት ለጋሽ ሀገሮች ሁሉ ያጋለጡት፣ የሚያውቁት የአደባባይ ሚስጥር ከሆነ ሰንብቷል።

በዚህ መሰሪ ወንጀል ያዝናቸው ብለው ከአሰሯቸው ተማሪዎች ውስጥ የቦኮ ትቤ ተወላጅ የሆነ ኑረዲን ሃሰን የተባለ የአለመያ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በድብደባ አሰቃይተው ከገደሉት በኋላ ራሱን ገደለ ብለው አስክሬኑን ለቤተሰቦቹ ሸጠውታል፡፡ በአሁኑ ወቅት ብዙ ተማሪዎች የደረሱበት እና የገቡበት ተፍጧል።

ይህ ሰቆቃ መጠኑን አልፏል! ግፍ በዚሁ እንዲቀጥል ከሆነ ደግሞ መቆም የሚችልበት ተግባር ባለመፈጸማችን ሁላችንም የዚያች ሀገር ልጆች ከታሪክ ወቀሳ እና ከህሊና ጸጸት አናመልጥም። ወያኔዎች በዘር ከፋፍለው በየተራ ስለሚያጠቁን ነው ይህ የሽብር አገዛዛቸው እድሜ ያገኘው። ይህን አደገኛ ክፍተት ካልዘጋነው መከራው ቀጥሎ ያሰቃየናል።

ግንቦት 7 የፍትህና የዴሞክራሲ ንቅናቄ አገራችን ይህን ሁሉ ግፍና መከራ ማስተናገድ እንዲበቃት ልጆቿ ተባብረን እንድንነሳ ደጋግሞ ጥሪውን ያቀርባል።

ለወያኔ የተመቸነው በየተራ ለመጠቃት አንዱን ብሄረሰብ በሌላው በማስፈራራትና ጥርጣሬ በመንዛት ለመግዛት የቀየሰው ዘዴ ሰለባ መሆናችን ነው።

ግንቦት 7 ንቅናቄ፤ የወያኔ የግፍ ቀንበር እንዲሰበር ሰፊ ህብረት ፈጥረን ከመታገል ውጪ አማራጪ የለንም ይላል።

የወያኔ ግፍ ይብቃ!

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
posted by Daniel tesfaye

Single Post Navigation

Leave a comment